Telegram Group & Telegram Channel
#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።



tg-me.com/orthodox1/13242
Create:
Last Update:

#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13242

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Export WhatsApp stickers to Telegram on Android

From the Files app, scroll down to Internal storage, and tap on WhatsApp. Once you’re there, go to Media and then WhatsApp Stickers. Don’t be surprised if you find a large number of files in that folder—it holds your personal collection of stickers and every one you’ve ever received. Even the bad ones.Tap the three dots in the top right corner of your screen to Select all. If you want to trim the fat and grab only the best of the best, this is the perfect time to do so: choose the ones you want to export by long-pressing one file to activate selection mode, and then tapping on the rest. Once you’re done, hit the Share button (that “less than”-like symbol at the top of your screen). If you have a big collection—more than 500 stickers, for example—it’s possible that nothing will happen when you tap the Share button. Be patient—your phone’s just struggling with a heavy load.On the menu that pops from the bottom of the screen, choose Telegram, and then select the chat named Saved messages. This is a chat only you can see, and it will serve as your sticker bank. Unlike WhatsApp, Telegram doesn’t store your favorite stickers in a quick-access reservoir right beside the typing field, but you’ll be able to snatch them out of your Saved messages chat and forward them to any of your Telegram contacts. This also means you won’t have a quick way to save incoming stickers like you did on WhatsApp, so you’ll have to forward them from one chat to the other.

Mr. Durov launched Telegram in late 2013 with his brother, Nikolai, just months before he was pushed out of VK, the Russian social-media platform he founded. Mr. Durov pitched his new app—funded with the proceeds from the VK sale—less as a business than as a way for people to send messages while avoiding government surveillance and censorship.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from vn


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA